Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሰሞነ ሕማማት ግጥምም ህህ ተተ ተዓ ተ ተተ ን መጋና ይህ መልእከት ለወገኖች እንዲደርስ ድጋፍ ያደረገልንን ወንድማችንን ይልማን አግዚአብሔር አምላክከ በነገር ሁሉ እርሱንና የእርሱ የሆነውን ሁሉ ይባርክ። የሚለውን ለማሳየት ኢትዮጵያዊ ሊቅ ተብሎ በሚወደሰው በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተዘጋጀውንና አርጋኖን የተሰኘውን መጽሐፍ ለመፈተሽ ተሞከሯል በዚህ ፍተሻ ትኩረት ለማድረግ የታሰበው መጻሕፍቱ የሚሰብኩት ማንን ነው። የሚለውን ለመመርመር ጥረት ተደርጓል በዚህም የተገኘው ውጤት አዋልድ መጻሕፍት አዘጋጆች ዓላማ ምንድን ነው። የእርሱ ሥራ ግርማ ላስታውስ ነው አልል ሁሌ በልቤ ነው ለሰው ነው እንዳልል ከቶ ምን ሊረባው። እርሱ ራሱ አምላከ ነው ወደ ማን ነው የሚያማልደን።
ያ ሸዘፈ ሰይጣን ለአግዚአብሔር የሚገባውን አምልኮ ለራሱ ለመውሰድ ሰዎች ጣዖትን እንዲያመልኩ ከማድረግም ሌላ ራሱን አውነተኛ አምላከ አስመስሎ ማቅረብን የሚጠቀም ቢሆንም የሚሠራው በእነዚህ መንገዶች ብቻ ነው ማለት አይደለም የማሳሳት ተግባሩን ለመከወን ሌሎችንም መንገዶች ጥበብ በተሞላበት መልኩ ይጠቀማል ከአነዚህ የማሳሳቻ መንገዶቹ ውስጥ ሌሎች ነገሮችን መላእክትን ሰዎችን አልያም ቁሳ ቁሶችን በፊታችን ላይ በማስቀመጥ በእነዚህ ነገሮች አማካይነት እግዚአብሔርን ቸል እንድንል ከዚህ ባስ ካለም አንድንረሳው ለማድረግ ይተጋል በተለይ በእኛ ቤተ ከርስቲያን ውስጥ ሰዎችን ለማሳሳትና ከፈቃደ እግዚአብሔር ለማራቅ ከሚጠቀምባቸው ነገሮች ውስጥ «አዋልድ» በሚል ስም የሚጠሩት መጻሕፍት ቀዳሚውን ስፍራ ይወስዳሉ ጥንተ ጠላታችን ሰይጣን ሰዎችን ለማጥመድ በቅዱሳን ስም የወረወረው የማጥመጃ መረቡ በሚገባ የሠራለት መሆኑን መመልከት የሚቻለው መረቡ ከጠበቀው በላይ በብዙ ዓሣዎች የተሞላ ቢሆንም ዓሣዎቹ ወደ ሞት እየተወሰዱ መሆናቸው አልገባቸውምና መረቡ ውስጥ መሆኑ ተስማምቷቸውና ተመቻቸተው መቀመጣቸውን ስንመለከት ነው በተደጋጋሚ አዋልድ መጻሕፍት ከመጽሐፍ ጋር የማይስማማ መልእከት አላቸው ከአግዚአብሔር ይልቅ ፍጡራንን ይሰብካሉ መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰብከውን ነገረ ድኅነት ፊት ለፊት የሚቃወምና ሰዎችን የማያድን መንገድ በማሳየት ይህ መንገድ ወደ መዳን ይወስዳል በሚል ያሳስታሉ የሚል ሐሳብ ቀርቧል ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ የመጻሕፍቱ ደጋፊዎች መጻሕፍቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆናቸውንና በመጽሐፍ ቅዱስ የሌሉ ታሪኮችን በማሳየት የመጽሐፍ ቅዱስን ጉድለት የሚሞሉ መጻሕፍት ናቸው በማለት ላይ ይገኛሉ በእርግጥ እንደተባለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ናቸውን። በቤተ ከርስቲያናችን ትምህርት እና አምነት አዋልድ የሚለው ስም የሚሰጣቸው መጽሐፍ ቅዱስን መስለው ከመጽሐፍ ቅዱስ ለተወለዱ መጻሕፍት ነው አዋልድ መጻሕፍት ከሊቃውንት መጻሕፍት ጀምሮ እስከ የጸሎት መጻሕፍት ድረስ የተደረደሩ ሲሆን ቤተ ከርስቲያን መጠናቸውን ለከታና ቀጥራቸውን ሰፍራ እነዚህ የእኔ ናቸው ከዚህ ውጭ ያሉትን ግን አላውቃቸውም ስላላለች በየጊዜው ደስ ያለው ሁሉ እየተነሣ የወደደውን በአዋልድ ስም ወደ ቤተ ከርስቲያን እንዲያስገባ አድሉን የሰጠች ይመስላል ለዚህም ምሳሌ አድርገን «ገድለ ቅድስት አርሴማ የተሰኘኙትን መጻሕፍት መጥቀስ እንቸላለን አርሴማ በተሰኘችው ሴት ስም የገቡት እነዚህ መጻሕፍት ያለ ምንም ችግር ተቀባይነት ያገኙና የቤተ ከርስቲያን መጻሕፍት የመምሰልን መብት የተቀዳጁ ቢሆንም የቤተ ከርስቲያን ፈቃድ አውቅና ይኑራቸው አይኑራቸው ግን ምንም ያሰፈሩት ነገር የለም ገድለ ቅድስት አርሴማ በሚል ስም የታተሙ ሁለት መጻሕፍት ሲኖሩ አንደኛው ባለቤቱ ያልተጠቀሰ እኔ ነኝ ባይ አዘጋጅ የሌለው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የሊቃውንት ጉባኤ አባል ነኝ የሚሉ ሰው ስም ሰፍሮበታል ይህ ደግሞ የስሕተት ትምህርትን የያዙ መጻሕፍት ወደ ቤተ ከርስቲያን ሰተት ብለው ሲገቡ የቤተ ከርስቲያን አስተዳዳሪዎች የመከልከሉን ቤተ ከርስቲያንን ከስሕተት ትምህርት የመጠበቁን ሥራ እየሠሩ አንዳልሆነ ሊያሳይ ይችላል ኪዳነ ምሕረት ቀጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት እግዚአብሔርን ማስረሳት ታላቁ መጽሐፍ መጽሐፍ ቅዱስ ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ መጨረሻው ድረስ የሚያስተምረው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር ነው ምንም እንኳ የተለያዩ ሰዎችን ሀገሮችንና ቁሳቁሶችን ቢያነሣም ይህን የሚያደርገው ግን ሰዎቹን አልያም ሀገሪቱን ማስተዋወቅ ስለ ፈለገ ሳይሆን በዚያ ውስጥ ስለ አግዚአብሔር ሊያሳይ የሚፈልገው ነገር ስላለ ነው በመሆኑም በቅዱሱ መጽሐፍ ውስጥ የሰፈሩ መላእከትም ሆኑ ቅዱሳን ሰዎች አልያም ንዋየ ቅድሳት ወይም ቦታዎች የአግዚአብሔርን ታላቅነት ማሳየት አንጂ የመሸፈንና የማስረሳት ሥራ ሲሠሩ አይታዩም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ ቀደም ሲል የነበሩ የቤተ ክርስቲያን አባቶች መጽሐፍ ቅዱስን ለማብራራት አልያም ወደ ቤተ ከርስቲያን እየገባ ያለውን የስሕተት ትምህርት ለመከላከል እንዲሁም ትምህርትና መልእከት ለማስተላልፍ በሚል ያዘጋጄቸው ልዩ ልዩ መጻሕፍት የእግዚአብሔርን ፍቅር ምሕረት ቸርነትና ለሰው ልጆች የሠራውን ድንቅ የማዳን ሥራ የሚያሳዩና ሰዎችን ወደ አግዚአብሔር የሚጠሩ መሆናቸው የሚታይ ነው በዚህም ውስጥ አግዚአብሔር ጎልቶ የሚታይ ሲሆን ጸሐፊዎቹም ሆነ ጸሐፊዎቹ የፈጠሯቸው ወይም በጽሑፎቻቸው ውስጥ ያሰፈሯቸው አካላት እግዚአብሔርን የሚከልሉና አነርሱ የሚታዩ አይደሉም በቀደመችው ከርስትና የሌሉ ከጊዜ በኋላ ወደ ቤተ ከርስቲያን የገቡና መጽሐፍ ቅዱስ የማያውቃቸው እንግዳ ትምህርቶች ወደ ቤተ ከርስቲያን ሾልከው ከገቡባቸው መንገዶች ውስጥ ዋነኛው አዋልድ መጻሕፍት ናቸው ስለ እነዚህ መጻሕፍት የሚነገረውና የሚታመነው መጽሐፍ ቅዱስን እንዲያብራሩና እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ስለ ሠራው ድንቅ ሥራ አንዲያስተምሩ ታስበው ነው የሚዘጋጁት የሚል ነው በአርግጥ መጻሕፍቱ የሚናገሩት አንደተባለው ነው ወይ። ዳንኤል ከብረት ዐዲስ አበባ መጋቢት እኛ የመጨረሻዎቹ እና ሌሎች በጽ ኪዳነ ምሕረት ቀጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት ለ አርጋኖን የተሰኘው መጽሐፍ በሰባቱ ዕለታት በሰኞ እስከ እሑድ የተከፋፈለ እያንዳንዱ ዕለትም በከፍልና በምዕራፍ የተደራጀ መጽሐፍ ነው በእያንዳንዱ ዕለት ጸሐፊው ወደ «ማርያም የጸለየው ጸሎት የሰፈረ ሲሆን አልፎ አልፎ ጸሎቱን ከመጽሐፍ ቅዱስ ምንባባት ጋር ለማስተሳሰር ጥረት ሲያደርግ ይታያልሸ ይህን መጽሐፍ መፈተሸ ያስፈለገበት ምከንያት መጽሐፉ ማንም ሰው በቀላሉ ሊያገኘው የሚቸለው በመሆኑ አዋልድ መጻሕፍት ምን ያህል እግዚአብሔርን እየሸፈኑት እንደ ሆነ ለማሳየት ጥሩ ናሙና መሆን ይችላል ተብሎ ስለታሰበ ነው የዓለም ሁሉ ቤዛ የሆነቸው ማርያም ቤዛ ማለት የተያዘን ወይም የተወሰደን ነገር ለማስመለስ የሚከፈል ዋጋ ካሣ ለውጥ መሆኑን የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ሲያስቀምጥ «ኢየሱስ ለሚያምኑበት ሁሉ በሞቱ ቤዛ እንደ ሆነላቸው አብሮ ያስነብባልሹ ኢየሱስ ለሰው ልጆች ራሱን ቤዛ አድርጎ ያቀረበ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በስፋትና በጥልቀት ያስተምራል ከዚህ በታች የሰፈሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባባት ቤዛ መሆኑን ለማሳየት ያህል ብቻ ተመርጠው የቀረቡ ናቸው ጥቅሶቹ ግልጽ የሆነ መልአከት ያላቸው በመሆኑ ማብራሪያ መሥራት አስፈላጊ ሆኖ አልተገኘም « የሰው ልጅም ሲያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም ማርቆስ « በውድ ልጁም አንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት» ኤፌሶን አንድ እግዚአብሔር አለና በአግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ እርሱም ሰው የሆነ ከርስቶስ ኢየሱስ ነው ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስከርነቱ ነበረ በኛ ጢሞቴዎስ እነዚህን እና መሰል የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባባትን እያየ ነገር ግን ከእነዚህ ሐሳቦች በተቃራኒ በመቆም ሥጋ የለበሰ ሁሉ መመኪያ ድንግል ሆይ ነፍስ የተዋሐዳቸውን ፍጥረት ሁሉ አከሊል የዓለም ሁሉ ቤዛ ነፍሴን ከክፉ ነገር ወደ ገሃነምም ከምትወስድ የጥፋት መንገድ አድኛት የሚለውን ጸሐፊ ሆነ ብሎ እያጠፋ ነው ከማለት ውጪ ምን ማለት ይቻላል ገጽ ጸሐፊው እዚህ ጋር ብቻ ሦስት ጉልሕ ስሕተቶች ሠርቷል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ የተጻፈ መሆኑን በመንገር መመኪያችን መሆን የሚገባው አግዚአብሔር ብቻ መሆኑን ሲያስተምር በኛ ቆሮንቶስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊትም በበኩሉ በአንተ የሚታመኑት ሁሉ ግን ። የሚለው በቀጣዩ ዕትም የሚፈተሽ ይሆናል የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ዐዲስ አበባ ስምንተኛ ዕትም የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ ኪዳነ ምሕረት ቀጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት ረርዮዳሙር ዴ መ ደስ ይላቸዋል ለዘላለሙ ደስ ይላቸዋል አነርሱንም ትጠብቃለህ ስምህንም የሚወድዱ ሁሉ በአንተ ይመካሉ በማለት ከእርሱ ውጪ ልንመካበት የሚገባ አካል ያለመኖሩን ያሳያል መዝሙረ ዳዊት በአርግጥስ ከእርሱ ውጪ ምን መመኪያ ሊኖረን ይትላል ነቢዩ ኢሳይያስም በበኩሉ «የእስራኤልም ዘር ሁሉ በእግዚአብሔር ይጸድቃሉ ይመካሉም ይባላል ኢሳይያስ በማለት የእስራኤል ዘር ሁሉ መጽደቂያቸውም ሆነ መመኪያቸው እግዚአብሔር መሆኑን ያሳያል «ስለዚህም ማንም በሰው አይመካ በኛ ቆሮንቶስ የአርጋኖን ጸሐፊ በቅዱሱ መጽሐፍ በተደጋጋሚ በዚህ መልኩ የሰፈረውን ይህን እውነት አልቀበልም ለማለት በሚመስል ሁኔታ ሥጋ ለለበሰ ሁሉ መመኪያ አድርጎ ያስቀመጠው ሥጋ ለባሽን ፍጡር መሆኑ «በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ከንዱ የሚያደርግ ልቡም ከአግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው የሚለውን ርግማን ስለማያውቀው ነው ወይስ ሕዝቡን በዚህ ርግማን ውስጥ ለመከተት። ሲያደርጉ ይታያሉ ይህም ፈጽሞ ከቃለ እግዚአብሔር የራቀ ሐሳብ ሲሆን ዕለት ዕለት ማስታወስ የሚገባንን እግዚአብሔርን ለማስረሳት የተሠራ የጠላት ሥራ መሆኑ ግልጽ ነው ማርያም የዓለም መድኅኒት መጽሐፍ ቅዱስ መድኀኒት ማን እንደ ሆነ ያስቀመጠው እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኀኒት ሊሆን እንደ ላከው አንመሰከራለን በሚል ነው ከዚህም ሌላ በአውነት ከርስቶስ የዓለም መድኀኒት እንደ ሆነ አናውቃለን ተብሎ ተጽፎ እናገኛለን በኛ ዮሐንስ ዮሐንስ አስትንፋሰ እግዚአብሔር የሆነው ቅዱሱ መጽሐፍ ከከርስቶስ ውጪ ምንም ዓይነት መድኀኒት የማያስተዋውቅ ቢሆንም የአርጋኖን አዘጋጅ ግን የዓለም ሁሉ መድኀኒት የምትሆን ብላቴና አግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ በማለት ሌላ የዓለም መድኀኒት ያለ በማስመሰል ሕዝብ የሚያሳስት ጽሑፍ አስፍሯል ገጽ ከዚህ ባስ ሲል ደግሞ የሕይወት መድኀኒት ምንጭ ሆይ የፈውስ መድኀኒት ውሃን ከአንቺ የሚቀዱ ሕመም ቁስለ ሥጋ ቁስለ ነፍስ የለባቸውም በማለት የመድኀኒት ምንጭ ሲያደርጋት የፈውስ መድኀኒት ውሃን ከእርሷ የሚቀዱ የሥጋም ሆነ የነፍስ ቁስል አይኖርባቸውም ይላል ገጽ ይህን ሐሳብ አያቀረበ ያለውን ሰው ከርስቲያን ነው ለማለት ይቻል ይሆን። ምከንያቱም በኢየሱስ አዳኝነት ያመነ ከርስቲያን ሌላ መድኀኒትን ሊሰብከ አይቸልም ምከንያቱም ቃሉ የባሕርይና የጸጋ ብሎ ሳይከፋፍል መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎቹ የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች የለምና የሐዋርያት ሥራ ሲል ዘግቶታል አትሞታልም እንደ አርጋኖን መጽሐፍ አዘጋጅ ማርያም የዓለም ሁሉ መድኀኒት የሕይወት መድኀኒት ምንጭ የፈውስ መድኀኒት ውሃ» ከሆነችና «ቁስለ ሥጋ ቁስለ ነፍስ ማዳን ከቻለች ሁለት መድኀኒት ያለን በመሆኑ ሐዋርያው እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኀኒት ሊሆን እንደ ላከው አንመሰከራለን በማለት ፈንታ ማለት የነበረበት «አኛም አይተናል አባትም እናቱንና ልጁን የዓለም መድኀኒት አንዲሆኑ አንደ ላካቸው እንመሰከራለን ነበር መልአኩም ቢሆን «ዛሬ በዳዊት ከተማ ከመድኅኀኒቷ መድኀኒት የሆነ ከርስቶስ ተወልዶላችኋልና ማለት ሲገባው «ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ከርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና ማለቱ ትልቅ ስሕተት መሆኑ ነዋ ሉቃስ ዝ በርግጥም ዓለም ሁሉ አንዲድን የተከፈለው ዋጋ አንድ ዋጋውን የከፈለውም አንዱ ከርስቶስ ብቻ ነው ከከርስቶስ ውጪ በጸጋም ይሁን በሌላ ዓለምን ለማዳን የሚቻለው ሌላ መድኀኒት በዚህ ምድር አልነበረም የለምም ኖሮ ቢሆን ከርስቶስ ወደዚህ ምድር መምጣትና መከራና ሥቃይ መቀበል የአብ ሥራ ግሩም ለተኣምረ ማርያም አትከራከር ገጽ ይህ ሐሳብ የአርጋኖን አዘጋጅ ብቻ ሳይሆን «ተኣምረ ማርያም በተሰኘው ከታብም ላይ «አመቤታችንን የዓለም ሁሉ መድኀኒት አድርጎ እንደ ፈጠራት ልብ አድርጋችሁ እነሆ ዕወቁ በሚል መስፈሩ ይታወቃል ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት በ ተኣምረ ማርያም ምዕራፍ ቀሩጥር ገጽ ኪዳነ ምሕረት ቀጥር አግዚአብሔርን ማስረሳት ሙን ባላስፈለገውም ነበር አንዲያውም በሥጋ ልደት የምትቀድመውና አንዳንዶች የጸጋ መድኀኒት ያደረጓት እናቱ ማርያም ባዳነችን ነበር ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር የመጣበት ምክንያት ምን እንደ ሆነ ወደ ዮሴፍ ተልኮ የነበረው መልአከ «ልጅም ትወልዳለች እርሱ ሕዝቡን ከጎጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ በማለት የሁላችን መድኀኒት ኢየሱስ መሆኑን አብስሯል ማቴዎስ ከዚህ ጋር በተያያዘ «እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ በሚል ያቀረበውም ኑፋቄ አብሮ ሊታይ የሚገባው ነው ጸሐፊው በዚህ ቦታ ላይ አግሯ ስር ተደፍቼ መስገድ አፈልጋለሁ ከማለትም በላይ ምንም እንኳ አሷ አሁን በዚያ ስፍራ ባትኖርም እሷ ያለፈቸበትንና የረገጥችውን አፈር ልሳም እያለ ነው ይህ ደግሞ አምልኮ ጣዖት መሆኑ ግልጽ ነው መጽሐፍ ቅዱስ እንኳን ሰውዬው በአካል ሳይኖር በአካል ቢኖርም ለየትኛውም ፍጡር መስገድ እንደሌለብንና ሊሰገድለት የሚገባው እግዚአብሔር አምላከ ብቻ እንደ ሆነ በማስጠንቀቅም ጭምር የሚያስተምር በመሆኑ ከርስቲያኑ ማኅበረሰብ እንዲህ ካለው ድርጊት ጋር ቢተባበር የአምላከን ትእዛዝ አልቀበልም ማለቱ መሆኑን መረዳት ይኖርበታል ዘጸአት በቤተ ከርስቲያን ትምህርትም ሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ እውቀቱ ጥሩ ነው በሚል በአንዳንዶች የአድናቆት ቃል እየቀረበለት ያለው የአርጋኖን መጽሐፍ አዘጋጅ መጽሐፍ ቅዱስ የዓለም ሁሉ መድኀኒት ኢየሱስ መሆኑን ያሰፈረውን አያወቀ ምነው ሴላ የማያድን መድኀኒት ሊያስተዋውቅ ሞከረ። ደግሞስ ለአምላከ ብቻ የሚቀርበውን አምልኮ ለፍጡር አንድንስጥ ኢ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መልእከት ምነው አስተላለፈ ቢባል ምከንያት ሆኖ የሚቀርበው እግዚአብሔርን ረስተን ሌላ ፍጡር ላይ በመደገፍ ከአግዚአብሔር ትእዛዝ ውጪ እንድንሆን ከመንግሥቱ እንድንጎድል ነው የሚል መልስ ቢሰጥ ምላሹ ተገቢ ይሆናል ነቢያት አንቺን ሊያዩ ወደዱ ግን አላዩም ይህ ሐሳብ እላቸኋለሁና እናንተ የምታዩትን ብዙዎች ነቢያትና ነገሥታት ሊያዩ ወደዱ አላዩምም የምትሰሙትንም ሲሰሙ ወድደው አልሰሙም ተብሎ ከተጻፈው ተወስዶ ባለቤቱ የተቀየረ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ያደረጉት ሰዎች ይረዱታል ሉቃስ የአብ ሥራ ግሩም ለተኣምረ ማርያም አትከራከር ገጽ ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ማለት መሆኑን ልብ ይበሉ ። ስግደትን በተመለከተ ጸሐፊው ምን ያህል ሰዎችን እያሳሳተ አንደሆነ በቀጣዩ ዕትም የሚቀርብ ጽሑፍ ይኖራል ፆ ለፈጣሪ የተጠቀሱ ጥቅሶችን ወስዶ ለፍጡር መስጠት ለአዋልድ መጻሕፍት ዐዲስ አይደለም የተለያዩ የቤተ ከርስቲያናችን መጻሕፍት በዚህ መልከ እየተቀየሩ የፈጣሪን ለፍጡር የሚሰጡ መሆኑን ለመመልከት በዲያቆን አግዛቸው ተፈራ የተጻፈውንና የተቀበረ መከሊት የሚለውን መጽሐፍ እንዲሁም በመሪጌታ ሠረቀ ብርሃን ዘወንጌል የተዘጋጀውንና «የዘመናት እንቆቅልሽ ሲፈታ ከፍል አንድ የተሰኘውን መጽሐፍ መመልከት ጠቃሚ ነው ኪዳነ ምሕረት ቀኦጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት ውሎርጮምር ዴዴ መ ትዐ መመ ታሪኩ የሚያስረዳው ሰብዓ የሜሆኑትን ሾመና ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው በሄዱበት ስፍራ ምን ማድረግ እንዳለባቸውና አንደሌለባቸው ወደ የት መግባት እንዳለባቸውና ለሚቀበሏቸው መናገር የሚኖርባቸውን አስረድቶ ላካቸው እነርሱም ሲመለሱ ደስ ብሏቸው «ጌታ ሆይ አጋንንት ስንኳ በስምህ ተገዝተውልናል አሉት አሱም ሊደሰቱ የሚገባቸው አጋንንት ስለተገዙላቸው ሳይሆን በሰማያት ስማቸው ስለ ተጻፉ መሆን እንዳለበት ነግሮ በዚያን ሰዓት ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሐሜት አደረገና የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ» ብሎ ካመሰገነ በኋላ «ወደ ደቀ መዛሙርቱም ዘወር ብሎ ለብቻቸው የምታዩትን የሚያዩ ዓይኖች ብፁዓን ናቸው እላችኋለሁና አናንተ የምታዩትን ብዙዎች ነቢያትና ነገሥታት ሊያዩ ወደዱ አላዩምም የምትሰሙትንም ሊሰሙ ወድደው አልሰሙም አለ ስለዚህ ይህ የኢየሱስ ንግግር ስለ ማርያም ሳይሆን ስለ ራሱ መሆኑ ግልጽ ነው የአርጋኖንም ጸሐፊ ይህ ይጠፋዋል ተብሎ አይታሰብም ነገር ግን ሐሳቡን ገልብጦና ለፍጡር ሰጥቶ አንዲህ የሚል መልእከት በገጽ ላይ አስተላልፏል ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን አንቺን ሊያዩ ወደዱ አላዩም ምሳሌሽን እንጄ የልጅሽን የመለኮትነቱን ምሥጢር ያየን አኛ ግን በቅድስት ጠረጴዛ ሥጋውንና ደሙን ቁርባኑን ተቀበልን አንድ አካል አንድ አምሳል በመሆናችን የተመሰገን ነን ሐሳቡ በቀጥታ ከወንጌል ላይ እንደተወሰደና መልእከቱ ተቀይሮ ለማይገባው ሰው ሊሰጥ እንደተሞከረ ቀደም ሲል የቀረበውን የወንጌሉን ቃል በመመልከት መረዳት ይቻላል ለዚህ ደግሞ ምከንያቱ እግዚአብሔርን ለማስረሳትና የአዳም ልጆችን ከአግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ ለማድረግ እንደ ሆነ ግልጽ ነው በሁሉ የምትገፒ በሁሉ ያለሽ በአንድ ጊዜ በሁሉ ስፍራ መገኘት የሚችል በተመሳሳይ ሰዓት በሁሉ ስፍራ ያለ ሁሉን ቻዩና የሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር አምላከ ብቻ መሆኑ ግልጽ ነው መዝሙረ ዳዊት ኢሳይያስ በእርግጥም በተመሳሳይ ሰዓት በሁሉ ቦታ መገኘት የሚችል ከእርሱ በቀር ማንም የለም ቀደም ሲል እንዳየነው የፈጣሪን አየወሰደ ለፍጡር በመስጠት ላይ የሚገኘው የአርጋኖን አዘጋጅ በሁሉ ቦታ የመገኘትን አቅም ከአግዚአብሔር ወስዶ ለማርያም ሲለግሳት ይታያል በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጥሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ የእግዚአብሔር ግን ማደሪያ አንቺ ነሽ በምድር ላይ የተሠራሽ በሰማይ የተቋፀርሽ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ የተዘረጋሽ ከባሕርም እስከ ባሕር ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር የሰፋሽ ገጽ በሁሉ ቦታ መገኘት የሚችለው አግዚአብሔር አምላክ ብቻ መሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት መመስከራቸውን ቀደም ሲል ቀርቧል ምከንያቱም አርሱ ብቻ ሁሉን ማድረግ የሚችል ታላቅ አምላከ ነውና መጽሐፍ ቅዱስ እንደመሰከረው በእርሱ ፊት የተሸሸገ የተደበቀ ምንም ነገር የለም ከአርሱ ውጪ ያሱ ሁሉ ፍጡራን በመሆናቸው በቦታ መወሰን በጊዜ መገደብ አለባቸው ኪዳነ ምሕረት ቀጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት ሙን በሁሉ ቦታ መገኘት አለመቻል ፍጡር የሆነችውን ማርያምንም የሚመለከት በመሆኑ ቀደም ሲል የአርጋኖን አዘጋጅ «ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ የተዘረጋሽ ከባሕርም እስከ ባሕር ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር የሰፋሽ በሚል ያለ አቅሟ ያሸከማት በሁሉ ስፍራ የመገኘት ችሎታ አይደለም የአዳም ልጅ ለሆነቸው ሥጋ ለባሺቱ ሴት ይቅርና መናፍስት ለሆኑት ለመላእከትም የሚቻል አይደለም ለዚህም ጥሩ ማሳያ የሚሆነው ማርያም የ ዓመቱን ልጄን ኢየሱስን ይዛ የፋሲካን በዓል ለማከበር ወደ ኢየሩሳሌም በወጡበት ወቅት የሆነው ነገር ነው በዓሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩና «ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር የአርጋኖን ጸሐፊ ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር የሰፋሽ ነሽ ያላት ማርያምና ዮሴፍ ኢየሱስ «ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት ባጤትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ቲመለሱ ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት እናቱም ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን። ወደ እግዚአብሔር የቀረብነው በፍጡር በኩል እንደ ሆነ በማስመሰል ያቀረበውም ሐሳብ ሌላው ስሕተቱ ነው ምከንያቱም ይህ ሐሳቡ በመጽሐፍ ቅዱስ ከሰፈረው ሐሳብ ጋር ሙሉ በሙሉ የማይስማማ ነውና መጽሐፍ ቅዱስ ምንም በማያሻማ መልኩ ወደ አብ ያቀረበን ኢየሱስ መሆኑን እንዲህ አስፍሮት ይገኛል አርሱ መርቶናልና ሁለታችንንም በመንፈስ ቅዱስ ወደ አባቱ አቅርቦናልና ኤፌሶን በ የታተመው ሰማንያ አሐዱ አጽንዖት የግል በዚህ ጥቅስ ላይ ለማየት አንደሚቻለው ወደ አባቱ ያቀረበን ኢየሱስ ነው ይሄውም እርሱ በሚል እንጂ እርሷ ተብሎ አልሰፈረም ይህን እያዩ ከመጽሐፉ ውጪ የሆነ ሐሳብ ማስተጋባት የከርስቶስ ደቀ መዝሙር ነኝ ከሚል ሰው የሚጠበቅ ሥራ አይደለም እናንተንም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁና ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ በፊት የተለያቸሁትን ከፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ ቁላስያስ አጽንዖት የግል በእርሱ በአግዚአብሔር ፊት የቀረብነው በኢየሱስ ሞት በኩል መሆኑን ሐዋርያው በዚህ ኪዳነ ምሕረት ቀጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት ከፍል ይናገራል አንዳንዶች በፍጡር በኩል ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንደምንቸል ምናልባትም ቀርበናል በማለት የሚያሰፍሩት ሐሳብ የከርስቶስን ሞት ከንቱ ማድረግና ከእርሱ ሞት የተሻለ ነገር እንዳለ በማስመሰል የሚሰብኩ በመሆናቸው ነው ይህም ጸረ ከርስቶስ የሆነ የትምህርታቸው አካል መሆኑ ግልጽ ነው ከርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንዲያቀርበን አርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞቸ አንድ ጊዜ በጎጢአት ምከንያት ሞቶአልና በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ በኛ ጴጥሮስ አጽንዖት የግል ቀደም ሲል እንደተባለው ወደ አግዚአብሔር የቀረብነው በከርስቶስ ኢየሱስ ሞት በኩል ነው ለዚህ ነው ሐዋርያው አንግዲህ ወንድሞች ሆይ በመረቀልን በዐዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት ከመካድና በጌታ ምትከ ፍጡርን ከማስቀመጥ በላይ እግዚአብሔርን የማስረሳት ሥራ ይኖር ይሆን። የእርሱ ሥራ ግርማ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ሕይወት ሊገነባ ከአብርሃም ዘር በመወለድ ለአዳም ልጅ ሁሉ ለመዳን የሚሆነውን የምሥራች ይዞ መጣ ሊያውም የሚደንቅ የምሥራት ዓለም ግን «የምሥራች ያለውን ጌታ «ምስር ብላ ብላ ከመቀበል ይልቅ ከሰፈር ውጭ ሰቀለቸው መድኀኒታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ለአኛ ራሱን አሳልፎ መስጠት ብቻ ሳይሆን ለሁላችን በኩር በመሆን ተነሣ ከዚያም ለሐዋርያቱ የምሥራቹን ሥራ ሰጥቶ በከብር ዐረገ ሐዋርያትም መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ በብዙ ቋንቋዎች የምሥራቹን ቃል አዳረሱት አሱ አግዚአብሔር የቋንቋ ባለቤት ነውና ሐዋርያት በሰው ሁሉ ፊት ቆመው ሲያገለግሉ አሜን በሚል ሊቀበሏቸው የወደዱትን የከርስቶስ ደቀ መዛሙርት ሲያደርጉ ሊሰሟቸውና ሊቀበሏቸው ያልፈለጉትን የእግራቸውን ትቢያ በማራገፍ ይለዩ ነበር የምሥራቹን አየሰሙ ያሉት ሰዎች ወንጌልን ከሰሙ በኋላ የሰሙትን መልካም ዜና ለመቀበልም ሆነ አልቀበልም ለማለት በሚገባቸው ቋንቋ ሐሳቡን መስማት ይኖርባቸው ነበር ከዚህም ሌላ ደቀ መዛሙርቱ አብረው ለማምለክ በሚሰበሰቡበት ጊዜ ሁሉም ሊሰማው በሚቹለው ቋንቋ አምልኳቸውን የሚያካሄዱ ምስጋናቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ሰሚውም ሊመሰገን የሚገባውን ጌታ በማመስገኑ በኩል ከእነርሱ ጋር ስለሚስማማ አሜን በማለት የአምልኮቱ ተሳታፊ ይሆን ነበር በቤተ ከርስቲያናችን ግን እንዲህ አልሆነም ለአምልኮት በእድሜም በትምህርትም በቋንቋም የተለያየ ማኅበረሰብ በአንድ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ይሰበሰባል በልማድ የሚያውቀው ቦታ ላይ ሲደርስ ወይም አሜን ሲባል ሲሰማ አሜን ይላል ለዚህ ደግሞ ምከንያቱ ቤተ ከርስቲያናችን የአምልኮ ቋንቋ አድርጋ የምትጠቀምበት ቋንቋ ግአዝ መሆኑና ሁሉም ለማለት አስከሚያስደፍር ድረስ የቤተ ክርስቲያናችን ምእመናን ለግእዝ እንግዳ በመሆናቸው ነው ግእዝ ምንም አንኳ የቤተ ከርስቲያንን አጥር ተከልሎ የሚገኝ ቋንቋ ቢሆንም ሁሉም ኢትዮጵያዊ የእኔ ቋንቋ በሚል ሊያጠናው የሚገባና ማደግ ያለበት ቋንቋ ነው በዘመናዊ ትምህርት ውስጥ የሚያልፍ ሁሉ እንግሊዘኛ ቋንቋን አንደሚማረው የግአዝ ቋንቋም በሁሉም ትምህርት ቤት አንድ ትምህርት ሆኖ ቢሰጥ ምንኛ መታደል ነበር ነገር ግን አይደለም በመንግሥትና በግል ትምህርት ቤቶች በቤተ ከርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ለምእመናን የግእዝ ቤተ ከርስቲያን ከመንግሥት ጋር በመነጋገር ይህን ለማድረግ የምትችልበት አድል ካለ ግእዝ አንደ አንድ ትምህርት እንዲሰጥ ጥረት ማድረግ ይኖርባታል ኪዳነ ምሕረት ቀጥር እግዚአብሔርን ማስረሳት ሙን ቋንቋ ትምህርት የሚሰጥበት እድል የሌለ በመሆኑ ካህናቱና አገልጋዮቹ በስብከተ ወንጌልና በዝማሬ ካልሆነ በቀር አብረው አሜን የሚሉበት እድል ጠባብ ነው ብዙሀኑ ከልጅ እስከ ትልልቅ ሰዎች ሴት ወንዱ ዘመናዊ ትምህርት የተማረውም ሆነ በቤተ ከህነት ትምህርት ያለፈው የሚሳተፍበት የቅዳሴ የኅብረት አምልኮ ጊዜን ማንሣት ይቻላል በአንድ ጊዜ ቤተ ከርስቲያናችን ባለችበት ስፍራ ሁሉ በሚካሄደው በዚህ የአምልኮ ጊዜ ምን ያህሉ የተባለው ይገባው ይሆን።