Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ የአረኞች ጥፋት ጥፋት ምንድን ነው። ስለዚህ እንደሜገባ ካልሠሩበት ካህን ቄስ ወይም ዲያቆን ተብሎ መጠራት ብቻ ከጥፋት አያድንም እንዲያውም በብዙ ያስጠይቃል የቅስናና የዲቁና መንፈሳውያን መስፈርቶችን አሟልቶ ማግልገልን የሚጠይቅ ነው። የቤተክርስቲያን መሥራች ክርስቶስ ኢየሱስ ከሚያምኑ ከሁሉም የሰው ዘር እንጂ በአካባቢ በቋንቋ የተገደበች አለመሆኗን ቀደም ሲል ተመልክተናል ራእይፁ ደቀመዛሙርቱን እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው ማቴ ማር በማለት ወደ ዓለም ሁሉ የላካቸው በሐዋርያት ትምህርት አምነው የተጠመቁት ሁሉ የአንዲት ቤተ ክርስቲያንን አያራቆትን መሆናችንን ተረድተንም በታሪክ ተወቃሾች በእግዚአብሔር ፊትም ተጠያቂዎች ከመሆናችን በፊት አካሄዳችንን ማስተካከል ያስፈልጋል ቆፍ የአንድነታችን ምስጢር ያለው እዚህ ላይ ነው። ስትል የጠየቀችው ለዚህ ነበር ዮሐ ይህ ሁሉ ታሪክ ከተፈጸመ ከሁለት ሺህ ዓመታት በቷኋላ ያውም በሠለጠነና የክርስትና ትምህርት በተስፋፋበት በዚህ ዘመን ከአንድ ጎጥ ተወልደውሩ አንድ ቋንቋ ተናግረው በሚኖሩና ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትናን በተቀበሉ አርቶዶክሳውያን መካከል ልዩ ወገን ናችሁ ማሰትና መባል በክርስትና ታሪክ እጅግ አሳፋሪና ኃላቀርነትም ነው።
የጥፋት ልጅ እግዚአብሔር የሰውን ጥፋት አይፈልግም መጥፋት ወይም አለመጥፋት እግዚአብሔርን እወቅ ከመሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እውቀት የጎደለበት የዮዩታሔ መሥዋዕት እንደ ድፍረት አይቆጠረብኝና በዘመናችን በአንዳንድ ካህናት ምክንያት የጠፉ ሕዝቦች ቁጥር እጅግ ብዙ ነው ይህ ደግሞ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ሰቤተ ክርስቲያናችን ጉዳት ነው ሕዝቡ ተስፋ የጣለባቸው ካህናት እረኞች ሃይማኖታዊ ጎላፊነታቸውን በተገቢው ሁኔታ ባልተወጡ ቁጥር ሕዝቡም በመንፈሳዊ ሕይወቱ ደካማና ተጎጂ እየሆነ መምጣቱ የማይቀር ነው ከብሉይ ኪዳን ሕዝብ የምናስተውለውም ይህን ምክንያትና ውጤት ነው በትክክል የእግዚአብሔር መልእክተኛ የሆነ አገልጋይ ከሁሉ በፊት ለጠፋው ሕዝብ ያዝናል የሚያስፈልገውንም ትምህርት ያስተምራል በላቀ አገልግሉቱ ስለሚታወቀው መጥመቀ መሰኮት ዮሐንስ አገልግሎች መጽሐፍ ቅዱስ ሲመሰክር የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ ይሳል ሉቃ መዳን በሰዎች ሕይወት ነግሦ እንዲኖር እንደ ውፃ ልክ ሆኖ የሚያገለግለው መንፈሳዊ አውቀት ቃለ እግዚአብሔር በመሆኑ ዛሬም የቀደሙት ካህናትና ሕዝብ ታሪክ ለሁላችንም ትምህርት ይሆነን ዘንድ በእነርሱ ታሪክ የአኛን ሕይወት ለመፈተሸና ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብ ለማድረግ ይህን አነስተኛ መጽሐፍ በፈቃደ እግዚአብሔር አዘጋጅቼአለሁ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ ከአዘጋጁ። ምዕራፍ አንድ ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል የእግዚአብሔር ቃል የምግብ ያህል ለሰው ልጆች ሕይወት ነው ዘዳ ማቴ ያለእንጀራ በሕይወት መኖር እንደማይቻል ሁሉ የቃሉን እውቀት ማጣትም እንደዚያው ነውና ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል ይላል እግዚአብሔር ሆሴ አለማወቅና ስንፍና ካለ ጥፋት አብሮ አለ ምሳ ኹ ቃሱን ስናውቅ እግዚብሔርን እናውቀዋለን አግዚአብሔርን ስናውቀው ደግሞ ለእርሱ እየተገዛን በሕይወት እንኖራለን ሕይወት የሚገኝበት እውቀት እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት ዮሒ ሕይወት የሚገኝበት የቃሱ አውቀት ለሁሉም አስፈላጊ ነው ይኸውም ክርስቶስ ነው ፊል ክርስቶስን በቃሉ መሠረት ካወቅን የተሰወረው የእግዚአብሔር ምስጢርና ጥበብ ሁሉ በእርሱ ይታወቃል ቁላኹ ቃል አግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን በነቢያትና በሐዋርያት የተጻፈው መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ይባላል ማቴሩ ጴጥዑ ክርስቶስ ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊት እግዚአብሔር በነቢያት በኩል በልዩ ልዩ መንገድ ተናግሮአል ወይም ቃሉን አስተላልፎአል ዕብ ይሁን እንጂ በነቢያት ሲነገር የነበረው የእግዚአብሔር ቃል ሰውን ሁሉ ወደ ክርስቶስ ለማድረስ ነበርና በዘመነ መጨረሻ ላይ ግን በራሱ በኢየሱስ ክርስቶስ ተናገረ ቁጋ በነቢያት የተዛራቸማቼ ቻ ባለመታዘዛቸው ምክንያት አንዴ ጠፉ ቃል በተባለ በክርስቶስ የተነገረውን የእግዚአብሔር ፈቃድና ሐሳብ የማትሰማ ነፍስም ትጠፋለች በዲ የሐዋሥ ቃሉን የሚሰማ ደግሞ ለዘላለም በሕይወት ይናራል የዮሐ ሓ እናስተውል አለማስተዋል ያለበት ሕይወት ከፍተኛ ጉዳት አለበት በነቢዩ ሆሴዕ በኩል ከተነገሩት ወቀሣዎች መካከል የሕዝቡ አስተዋይ አለመሆን አንዱ ችግር ነበር በፈጣሪያቸው ላይ የሚፈጽሙአቸው በርካታ ኃጢአቶች ነበሩ ማስተዋል የሚባል ነገርም በፍጹም አልነበራቸውም ወደ ጥፋት የሚመራቸውም አለማስተዋላቸው ነበር ስለዚህ የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል አለ ሆሴ ሓ ይህን ነገር የሚያስተውል ጠቢብ የሚያውቃትም አስተዋይ ማን ነው። ሀ ወንጌል እናሳልማለን እንጂ ወንጌል አላስተማርንም ቃለ ወንጌልን አለመማር አለመስማት አለማንበብ አለማስተዋልና አለመታዘዝ ካለ ምንጊዜም ቢሆን የመዳናችንን መንገድ እየዘጋነው መሆኑን ማወቅ ይገባናል ዮሐ ማቴ ዮሐ የወንጌል ዓላማው በሰዎች ልብ ተቀምጦ ሰዎች እንዲጠቀሙበት እንጂ እንዲሰሙት ብቻ አይደለም በቤተ ክርስቲያናች የሥርዓተ አምልኮት መጻሕፍት ሣክበረ የወንጌልን ቃል ሰምተን እንሠራ ዘንድ ክቡር የሚሆን የወንጌልን ቃል በልቡናችን ትጽፍ ዘንድ ወዘተ ተብሎ ተጽፎ እናገኛለን ሥርዓተ ቅዳሌሴ አንድ አባት ካህናትን ሲያስተምሩ ሕዝቡን ወንጌል ማሳለም እንጂ ወንጌልን አላስተማርንም በእግዚአብሔር ቃል እጦት ለሚጠፋው ሕዝብ እያንዳንዳችን ተጠያቂዎች ነን ማለታቸውን ስስታውሳለሁ በእርግጥ የተነበበውን ቅዱስ ወንጌል መሳለሙ ለቃሉ ክብር ከመስጠት አኳያ ስለሆነ የሚነቀፍ ባይሆንም የሰማነው ቃለ ወንጌልና የተሳለምነው ወንጌል በልባችን ተጽፎ የማይቀመጥና መሳለም ብቻ ከሆነ መምህሩ እንዳሉት ከጥፋት አያድንም ብዙ ሰው ቅዱስ ወንጌልን ይሳለማል መስቀሉን ይሳለማል ቤተክርስቲያንን ይሳለማል አነዚህን መሠረታዊያን የክርስትና ሕይወት ምስጢሮችን በማስተማር በአፉ የሚስመውን ወንገል በልቡም አንዲያስቀምጠው የማድረግ ኃላፊነት አለብን በክንድ ወቅት በየመንገዱ ሳይቀር የአባቶችን መስቀል የተሳለሙ በየጠዋቱ ቤተ ክርስቲያን ሳይሳለሙ የማይውሉ የነበሩሩ ወንጌሉን ተሳልመው ጸበሉን ጠጥተው የመፄድ ልምድ የነስራቸው ብዙዎች ዛሬ በዚያው ሕይወት የሉም። አንዳንድ የታሪክ መዛግብት የሚያስረዱን እንጂ በዘመናችን የከበረ ስሙን ቀለል ባለ ልማዳዊ አገላለጽ ኢየሱስ ጌታ ነው በኢየሱስ ስም ኢየሱስ ያድናል እንደማለት የተገለጸ አይደለም በተለይም የሮማ ቄሳሮች በክርስቲያኖች ላይ ይፈጽሙባቸው የነበረው ስቃይና ግፍ በአነዚህ የመከራ ዘመናትም ቤተ ክርስቲያን ያሳለፈችውን የሰቆቃ ታሪክ ስናስተውል ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም መመስከር ምን ዓይነት እንደሆነ እንረዳለን የሸዋ ሊቀጳጳች የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የቤተክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ በተሰኘው መጽሐፋቸው የሮማ ነገሥታት በቤተ ክርስቲያን ላይ ያደረሱትን ዕልቂትና ሥቃይ በመዘርዘር ቤተ ክርስቲያን አግዚአ ክርስቶስ ነው ስትል የሮማ ቄሣሮች የመከራው ዓይነትና ብዛት እየጨመረ ሄደ እንዲያውም የክርስቲያኖችን ዕልቂትና ሥቃይ የሮማ ቄሣሮች በመዝናኛና በዕረፍት ሰዓታቸው ይመለከቱት ነበር ብለዋል ገጽ እንዲያም ሆኖ ግን የኢየሱስ ክርስቶስን የጌትነቱን ስም ማንሣትና መመስከርን አላቆሙም ነበር ኢየሱስ ጌታ ነው ብለን መመስከር ለማንና የት መሆኑን ጭምር የምንማርበት ታሪክም ነው የመጀመሪያዩቱ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በእርግጥ የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ የሆነ ሁሉ ስለ ስሙ መመስክር አለበት የሐዋሥ በሰው ፊት የማይመሰክርለትን ሁሉ እርሱም በሰማያት ባለው አባቱ ፊት ይክደዋል ማቴ ነገር ግን ሁሉም በአግባብና በሥርዓት እንደ ቃሉ ሲፈጸም እንጂ አለቦታው ከሆነ ኢየሱስ ጌታ ነው የሚለው የከበረውን ዕንቁ በእሪያ ፊት መጣልም ይሆናል እንዲህ ያለው ሁሉ የክርስትናው አውነትና አውቀት ገብቶት ነው ማለትም አይቻልም የአረኞቻቸው ጥፋት የእግዚአብሔር ሕዝብ በእውቀት እጦት ለጥፋት የተዳረገበት ዋና ምክንያት መንፈሳዊ ኃላፊነቱን የተቀበሱት ነቢያቱና ካህናቱ የእረኝነት ኃላፊነታቸውን ባመለወጣታቸው ነው « በሐሰትም የሚያስተምር ነቢይ እርሱ ጅራት ነው። በጠበበው ደጅ ግቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ለሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙ ናቸው ይላል ማቴ ቃሉ እያንዳንዱ ሰው መንገዱንና ኑሮውን በማየት በየትኛው መንገድ ላይ መቆሙን እንዲያስተውል ይጋብዛል ምዕራፍ ሦስት እግዚአብሔርን እወቅ በአግዚአብሔር መልክ የተፈጠረው ሰው ፈጣሪውን አለማወቁ ከሁሉም የሚከፋ ኃጢአት ነው የእግዚአብሔር ሕዝብ ፈጣሪውን ባለማወቁ ከእንስሳት አንሶ ስለተገኘ እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ የተናገረውን ቃል ነቢዩ እንደሚከተለው ጽፎታል አግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማይት ስሙምድርም አድምጪ ልጆችን ወለድሁ አሳደግሁም እነርሱም ዐመሁብኝ በሬ የገዥውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ እስራኤል ግን አላወቀም ሕዝቤም አላስተዋለምሸ ኢሳ ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድ እኔም እንደሆንሁ ታስተውሉ ዘንድ እናንተ የመረጥሁትም ባሪያዬ ምስክሮቼ ናችሁ ይላል እግዚአብሔር ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም ከእኔም በኋላ አይሆንም እኔአኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም ኢሳ ብቸኛ አዳኝ የሆነውን እግዚአብሔር ማወቅ ለስው ሁሉ ዕረፍትና ሰላም የሚገኝበት መንገድ ነው የእግዚአብሔር ሕዝብ ተብሎ እግዚአብሔርን አለማወቅ አንዴት አሳዛኝ ነው። ይህ ደግሞ ዓላማዊ ጠባይ ነው አግዚአብሔርን የማያውቅ እግዚአብሔርንም የማያሳውቅ የእግዚአብሔር ሕዝብ የለም የእግዚአብሔር ሰው ዳዊት የአባትህን አምላክ እወቅ ሲል ሰሉሞንን አዞታል ዜና እግዚአብሔርን ሳያውቁ እንደፈቃዱም ሳይኖሩ የሚፈጽሙትን ሃይማኖታውያን ሥርዓቶች ሳይቀሩ በአግዚአብሔር ፊት ተነቅአዋል ከመሥዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ ሰዎች ሃይማኖታዊ ሥርዓትን አስመልክተው ለአምላካቸው የሚያቀርቡአቸው ስጦታዎች መሥዋዕት በሚለው ቃል ሊጠቃለሉ ይችላሉ መሥዋዕት በመጽሐፍ ቅዱስ ሰፊና ዝርዝር ታሪክ ያለው ሲሆን በዚህ ነጥብ ሥር እንድናየው የተፈለገው ግን ከመሥዋፅት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ መቅደም እንደሚገባው ነው ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እወዳለሁና ሆሴ በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው አግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን። የእግዚአብሔር መልእክተኛ የሆኑት ካህናት በታማኝነት ሕዝቡን ካለማስተማራቸው ነ የተነሣ እኔ ደግሞ በሕዝቡ ሁሉ ፊት የተናቃችሁና የተዋረዳችሁ እድርጌአችሏለሁ ሲል እግዚአብሔር እንደገና በነቢዩ ሚልኪያስ በኩል ካህናቱን እንዴት እንደ ገሠጻቸው እናያለን ሚል እግዚአብሔር በትእዛዙ የሚሄዱትን ያከብራል ከትእዛዙ ውጪ የሚኖሩትን ደግሞ ይንቃል ያዋርዳልም ሳሙ በተለይም ሰአንድ መንፈሳዊ ኃላፊነት የተጠራ አገልጋይ በእግዚአብሔር ፊት ተጠልቶ ተንቆና ተዋርዶ ማየት ከምንም በላይ አሳዛኝ ነው ይ ካህናቱን ስለሕጉ ጠይቅ ተብሎአል ጣልተማሩ አያውቁ ካላወቁ አይጸደቁ የእግዚአብሔር ሕዝብ ማወቅ የሚገባውን እንዲያውቅ ካህናቱ ሕጉን በትክክል እንዲያስተምሩ ታዘዋል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ካህናቱን ስለ ሕጉ ጠይቅ ሐጌ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹምና ቅዱስ እንደ መሆኑ መዝ ሮሜ የካህናቱ ድርሻ ይህን ቅዱስ ቃል ነገር ግን ክህነታዊ ኃላፊነታቸውን እንዲሉ ለሕዝቡ ማሳወቅ ነበር ባለመወጣታቸው ተወቅሠዋል ለአምላካቸው መስጠት የሚገባቸውን ክብርም ትተዋልና እናንተ ስሜን የምታቃልሉ ካህናት ሆይ ልጅ አባቱን ባሪያም ጌታውን ያከብራል እኔስ አባት ከሆንሁ ክብሬ ወዴት አለ። እንደ መልከ ጴዴቅ እንደ አሮን እንደ ዘካርያስና የመሳሰሉ የእግዚአብሔር አገልጋይ ካህናትና ሊቃነ ካህናት የመኖራቸውን ያህል ካህናተ ጣዖታት የሚባሉም አሉ ሶፎ ቁ በብሉይም ሆነ በሐዲስ ዘመን ብዙ ዓይነት ካህናት እንደ ነበሩ መጽሐፍ ቅዱስ ይተርካል ርኅራቴጌ የሌላቸው ካህናት ነበሩ ሉቃ ሩ ከዐመፅ ጋር የሚያብሩ ካህናት ነበሩ ማቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀልና መሞት ዋናዎቹ አቀንቃኖች ካህናት ነበሩ ማቴ ልዩ ልዩ የሃይማኖት ቡድን መሪዎችን ጨምሮ ካህናቱ ሕዝቡን በማነሣሣትና በማባበል የክርስቶስን ሞት እውን ለማድረግ ከፍተኛውን ሥራ ሠርተዋል አብዛኛው የጥፋት ሥራ በእነዚህ ካህናት ቅንብር መከናወኑን ስናይ አንተም እውቀትን ጠልተፃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላፃለሁ የሚለውን መለኮታዊ ቃል እንደገና አንድናስታውስና ካህናት ክህነታቸውን በተገቢው መንገድ ካልተጠቀሙበት በእግዚአብሔር ፊት የሚጠሉ መሆኑን ለአዲስ ኪዳን ካህናትም አገልጋዮች የሚያስተምረው ዓቢይ መልአክት አለው ክህነቱ ሲለወጥ ሕጉ ደግሞ ሊሰወጥ የግድ ነው ረጅሙን የብሉይ ኪዳን ታሪክ ስንመለከት የክህነት አገልግሎቱ ደካማ ነበረ ሕጉም ሆነ መሥዋዕቱ ፍጹምነት የጎደለው ስለነበረ ፍጹም ድኀነት አልተገኘበትም በአዲስ ኪዳን ግን አዲስ የክህነትና የመሥዋዕት ሕግ ተመስርቶአል ሐዋርያው ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱ እንደ ገለጸው እንግዲህ ሕዝቡ በሌዊ ክህነት የተመሠረተን ሕግ ተቀብለዋልናል በዚያ ክህነት ፍጹምነት የተገኘ ቢሆን እንደ አሮን ሹመት የማይቁጠር እንደ መልከ ጴዴቅ ሹመት ግን የሆነ ሌላ ካህን ሊነሣ ወደ ፊት ስለ ምን ያስፈልጋል። አንድ አገልጋይ ለዚህ መንፈላዊ ኃላፊነት ሲታጭ ወይም ኃላፊነቱን ሲቀበል ምንም እንኳን የኃላፊነቱ ተዋሪድ ቢለያይም ምዕመናንን ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የመሪነት ስፍራ እየተሰጠው መሆኑን ሊያውቅ ይገባል በዚህ የቤተ ክርስቲያን የመሪነት አገልግሎት ጳጳስኤሏስ ቆጳስ ቄስ እና ዲያቆን ተብሰው በደረጃ የተቀመጡት ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቁልፍ ኃላፊነት ሲኖ ራቸው ብቃታቸውና መመዘኛ መስፈርታቸውም በቅዱስ መጽሐፍ እንደሚከተለው ሰፍሮአል በእርግጥ እነዚህን መስፈርቶች የነፍስ አባትና የነፍስ ልጄ የመሆን ምስጢር ክፍል ሁለት መጽሐፌ ላይ የገለጽኩአቸው ቢሆንም በአጭሩም ቢሆን እንደገና ለመግለጽ እሞክራለሁ ምክንያቱም እነዚህ መንፈሳውያን መስፈርቶች የሴሉባት ቤተ ክርስቲያን ሊወድቅ እንደ ዘመመ ቤት አደጋ የተጋረጠባት ስለምትሆን ስለ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አስተዳደር በቂ ግንዛቤ እንዲኖር ማድረግ ይገባል መስፈርቶቹ የሚገኙት በኛ ጢሞቴዎስ ም ቁ ባለው ክፍል ውስጥ ነው ፕጥማይነቀፍ ይላል ቤተክርስቲያንን ለነቀፋና ለክስ የማይዳርግ በሕይወቱ ዙሪያ ነቀፋ የሌለበት መሪ አገልጋይ መሆን አለበት አንዲት ሜስት ባል ፈት ያልሆነና በአንዲት ሚስት ጋብቻውን ያጸና እንጂ እየፈታ የሚያገባ መሪ እንዲሆን አልተፈቀደም ይህ መመሪያ ዲያቆናትን ጨምር ያካትታል ከአንዲት ሚስት በላይ ማግባት ለሁሉም ክርስቲያን ያልተፈቀደ ቢሆንም የቤተ ክርስቲያን መሪዎች አገልጋዮች ይበልጥ አርአያ መሆን ይጠበቅባቸዋል። ነገ እንደተባለው በሁለት አሳብ ተጠምደው በማንከስ የሚኖሩ አሉ ከሁሉም ይልቅ የሚያሳዝነው አጽራረ ቤተ ክርስቲያንን አስታግሥልን በማለት እየጸለዩ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶችና ለሕዝባችን ወደ ሌሎች የአምነት ተቋማት መፍለስ ምክንያት የሆኑት የአንዳንድ ካህናት ጉዳይ ነው ዕውርም ፅውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድዓድ ይወድቃሉ የሚለው ቃለ ወንጌል እንደዚህ ዓይነቶቹን ነው ማቴ ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም ኢሳ ተብሎ እንደተጻፈው ከእውቀት ማጣት የተነሣ ከገጠር እስከ ከተማ ካለው ብዙ ሕዝብ መካከል ሰልዩ ልዩ ከንቱ አምልኮ የሚገዛ ነው እንዲህ ስቶ ለሚገኘው ሕዝብ ካህናቱ አለመድረሳቸው ደግሞ ከምንም በላይ አሳዛኝ ነው እስኪ በትንቢተ ኢሳይያስ ያለውን ደግሞ አንመልከት «የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል እኔ ፊተኛ ነኝ እፄም ኋለኛ ነኝ ከእኔ ሌላም አምሳክ የለም እንደ እኔ ያለ ማን ነውገ። ይህን እውነት ያልተገነዘቡና ቤተክርስቲያን ማለት የልዩ ልዩ ሕዝቦች ስብስብ መሆኗን ያልተረዱ ያላወቁ አንዳንድ ወገኖቻችን ቤተ ክርስቲያን በየሀገሩ የምትስፋፋበትንና የምትበዛበትን መንገድ በመዝጋት በአጉል ፃይማኖታዊ ቅናት ቤተክርስቲያንን የጠቀሙ መስለው እየጎዲት ያሉ ብዙዎች ናቸው የቤተ እስራኤላውያን ታሪክ በቤተ ክርስቲያናችን ካህናት አይታ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሁለት ላይ እንደተገለጸው ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ የተመሠረተችው በቤተ እስራኤል ነው በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ምድር የተመሠረተችው ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ትምህርት በዓለም ሁሉ እየተስፋፋች አብያተ ክርስቲያናት እየተበራከቱ የክርስቲያኖች ኅብረትም እየጨመረ እያደገ መምጣቱን ከቅዱሳት መጻሕፍት መረዳት ይቻላል ቀደም ሲል እንዳየነው ክርስትናን በመቀበልና በማስፋፋት ረገድ ሀገራችን ኢትዮጵያ በግንባር ቀደምትነት ትጠቀሳለች ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድመ ታሪክዋን የሚያደበዝዙ ክርስቲያናዊ መስለው የቤተ ክርስቲያንን እውነተኛ ተልዕኮ የሚያቀጭጩ ልማዶች በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች መኖራቸው በተለያየ መንገድ የተነገረበትና የተገለጸበት ሁኔታ አለ በተለይም ከቤተ እስራኤል ጋር ከፍተኛ የሆነ ፃይማኖታዊ ትስስር ያላት ሀገራችን ብኩ እስራኤላውያን ያዶባተም ጭምር ናትና ቤተ እስራኤላውያን ክርስቲያኖች ሆነው የቤተ ክርስቲያን አግልግሎት ለመስጠት እየፈለጉ እናንተ አትፈለጉም እየተባለ ተግልለው መኖራቸው ከየአቅጣጫው ሲነገር ይሰማል በኢትዮጵያ ስለሚገኙት ቤተ እስራኤላውያን መገለል ጥላቻ ስድብና ልዩ ልዩ ከበድ ያሉ የመከራና የሥቃይ ኑሮን እንደገፉ የሚያሳይና ዝርዝር ብሶት ያለበት መስፍን አስፋ የተባሉ ቤተ እስራኤላዊ የጻፉትን አሊያህ ቤት የተሰኘውን መጽሐፍ ከአንድ ወንድም እንደ አጋጣሚ አግኝቼው ተመልክቼው ነበር። ጸሐፊው ስለ ቤተ እስራኤላውያን ቅስናና ድቁና አይቀበሉም ቤተክርስቲያን ገብተው በማንኛውም የክህነት አገልግሎት እንዲሳተፉ ስለማይፈቅድላቸው ነው ብለዋል ዯክርስቲያን ሀገር በምትባለው ራችን እንዲህ ዓይነት ኢክርስቲያናዊ ተግባር ሲፈጸም ማየትና መስማት ለእውነተኛ ዱዳ ክርስቲያን ሁሉ አሳፋሪ ነው ከቤተክርስቲያኒቱ በየጊዜው እየፈለሱ በሚሄዱት መቆጨት ሲንባን ከእናንተው ጋር እንሁን እንቀድስ እናገልግልየሚሉትን አንፈልጋችሁም የእኛ ቤተ ክርስቲያን አባላት አትሆኑም ማለት የክርስቶስን ሞት ከንቱ ለማስቀረት እንደመሞከር ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው የተለያዩትን ሕዝቦች በደሙ አንድ ለማድረግ ነው ኤፌ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ በማንሣት ቅዱስ አባት ሆይ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው ሁሉም አንድ ይሆኑ ዝንድ በማለት ወደ ባሕርይ አባቱ ጸልዮአል ዮሐ እና ይህም ጸሎቱ በእርሱ አምነው ስለሚከተሉት ክርስቲያኖች ሁሉ የቀረበ ው አንድ መንጋ ይሆናሉ አረኛውም አንድ ያለውም ለዚህ ነው ዮሐ ጌታ አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመመሥረት ደሙን ሲያፈስ ጠላት ዲያብሎስ ደግሞ አንድነቷን ለማፍረስ ይተጋል የቤተ ክርስቲያን አንድነት ምን እንደሆነ ያልተረዱ አንዳንድ ሰዎች ታዲያ ሳይታወቃቸው በአጉል ቅናት ተይዘው የዲያብሎስ ጉዳይ አስፈጻሚ ሲሆኑ ይታያሉ ይህን እውነት ያልተገነዘቡ ሰዎች ጸሐፊው እንደገለጹት በልማድ ፈላሻ የሚባሉት ወገኖች በቅዳሴ ጊዜ አብረው እንዳይቀድሱ በመከላከልና እንደ ልዩ ወገን በመቁጠር ክርስቶስ በደሙ የመሠረታት ቤተክርስቲያን አንዳትስፋፋ ማነቆ ይሆናሉ ከዚሁ ጋር የተያያዘ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአንድ ሀገረ ስብከት ሥር የተፈጸመ አንድ ታሪክ ሰምቻለሁ ፈላሻ ከሚባሉት ወገኖች መካከል ቀሳውስትና ዲያቆናቱን ከእኛ ጋር አብራችሁ አትቀድሱም በሜሱ የአንድ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ካህናት መካከል በተፈጠረው ከፍተኛ አለመግባባት ጉዳዩ ከሀገረ ስብክት ጽቤት እስክ ዞን መስተዳድር ጽቤት ከዚያም እስከ ክልል ጽቤት ደርሶ ለብዙ ዓመታት እያጨቃጨቀ ብዙ ተደክሞበታል። ባሉት ጊዜ ጌታ ግን በመገሠጽና ምን ዓይነት መንፈስ አንደሆነላችሁ አታውቁም የስው ልጅ የስውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም ሉቃ ያሰበትን ታሪክ እንድናስታውሰው ግድ ይላል አዚህ ላይ የደቀ መዛሙርቱ አሳብ ከጌታችን አሳብ ፍጹም የተለየ መሆኑን እናያለን ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ሁሉ በምሕረቱና በይቅርታው ከጥፋት ሊያድን የመጣ መሆኑን ዘንግተው ለስማርያ ሰዎች ቁጣና ቅጣት ተመኙላቸው ጌታ ግን የተሳሳተ አሳባቸውን በማረምና በመገሠጽ ለሰው ያለውን ምሕረትና የመጣበትን ዓላማ ገለጸላቸው ብ ያዕቆብና ዮሐንስ በራሳቸው አሳብ በመመራት ጌታችን ወደዚህ ዓለም የመጣበትን ዓላማ እስከ መዘንጋት እንደ ደረሱ ሁሉ በዘመናችን ያሉ አንዳንድ ካህናትም ያወቁ መስለው ባለማወቅ ቀንበር ሥር በመውደቃቸው ምክንያት እየፈጠሩ ያለው ችግር ከፍተኛ መሆኑ የታወቀ ነው ያዕቆብንና ዮሐንስን ጌታ እንደ ገሠጻቸው ቤተ ክርስቲያንን የጠቀሙ መስለው ቤተ ክርስቲያንን እያፈረሱ ያሉ ካህናትንም ሆነ ምዕመናንን በእግዚአብሔር ቃል ማረምና መገሠጽ የሚችል የባላይ ኃላፊ አስፈላጊ ነው ይህ ካልሆነ ግን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነትና እድገት ራሳችን በራሳችን ጠላት እየሆን ነው እናገልግል የሚሉትን አእየገፋንና ቤተ ክርስቲያንን አያራቆትን መሆናችንን ተረድተንም በታሪክ ተወቃሾች በእግዚአብሔር ፊትም ተጠያቂዎች ከመሆናችን በፊት አካሄዳችንን ማስተካከል ያስፈልጋል ቆፍ የአንድነታችን ምስጢር ኢየሱስ ክርስቶስ ልዩነትን በማስወገድና የጥል ግድግዳ የተባለውን በእግዚአብሔርና በሰው በሰውና በሰው መካከል የነበረውን ልዩነትን በሥጋው በማፍረስ አንድነትን መሥርቶአል ይህም የሆነው አንድን አዲስ ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው።